
- Details
ዕጩ ዶ/ር አሸናፊ ኃይሉ የ3ኛ ዲግሪ መመረቂያ ጽሑፉን የውስጥና የውጭ ገምጋሚዎች በተገኙበት ጥር 03/2015 ዓ.ም አቅርቧል፡፡
ዕጩ ዶ/ር አሸናፊ ያቀረበው የመመረቂያ ጽሑፍ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በአየር ንብረት ለውጥ፣ በምግብ ዋስትናና በገጠር አኗኗር መተዳደሪያ ዕቅድ ዙሪያ “Climate Variability, Smallholder Rural Households’ Economic Base and Food Security Status in North Shewa, Oromia Region, Ethiopia” በሚል ርዕስ ላይ የተከናወነ ነው፡፡ ተጨማሪ ምስሎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

- Details
ከጋሞ እና ጎፋ ዞኖች እንዲሁም ከደራሼና ባስኬቶ ልዩ ወረዳዎች ለተወጣጡ 30 የደቡብ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የሴቶች ሊግ መካከለኛ ሴት አመራሮች የአመራርነትንና የተግባቦት ክሂሎትን ለማሳደግ የሚያስችል ሥልጠና ከጥር 3-4/2015 ዓ.ም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ምስሎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

- Details
በኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ አመራር ዝግጅት ምልመላና ስምሪት ሥርዓት ማስተግበሪያ መመሪያ መሠረት በዩኒቨርሲቲው ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ቦታ በተደረገው ግልጽ ውድድር መሠረት የዩኒቨርሲቲው የሥራ አመራር ቦርድ ከታኅሣሥ 22/2015 ዓ/ም ጀምሮ ዶ/ር ቦጋለ ገብረማርያም የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ሆነው እንዲያገለግሉ የኃላፊነት ሹመት ሰጥቷል፡፡
Read more: ዶ/ር ቦጋለ ገብረማርያም የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙ
- Details
The editorial board of OMO International Journal of Sciences would like to invite researchers, experts, academia, and entrepreneurs to submit manuscripts of original research, review articles, technical notes and short communications for publication in the journal. OMO Int. J. Sci. is Arba Minch University based journal which publishes top-level research works from all areas of Natural, Computational, Agricultural, Veterinary, Food, Medical and Health Sciences.

- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ በጎፋና ኮንሶ ዞኖች እና በደራሼ ልዩ ወረዳ በዝናብ እጥረት በተከሰተ ድርቅ ለተጎዱ ወገኖች የሚውል 2.1 ሚሊየን ብር የሚያወጣ የምግብ እህል ድጋፍ ከታኅሣሥ 26-28/2015 ዓ/ም በየሥፍራዎቹ በመገኘት አስረክቧል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ