
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የስነትምህርትና ስነባህሪ ሳይንስ ት/ቤት ለዩኒቨርሲቲው ተደራሽ በሆኑ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች በሚገኙ ት/ቤቶች የትምህርት ስኬቶችና ተግዳሮቶች ዙሪያ የትምህርቱ ዘርፍ ባላድርሻዎች ምክክር እና የተማሪዎችን ውጤት በማሻሻል ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሠራ ታላቅ የምርምር ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ጥር 20/2015 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

- Details
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የድርጅቱና የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የሰባት ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ሳይንቲፊክ ዳይሬክተሮች በተገኙበት ጥር 20/2015 ዓ/ም ዓመታዊ ጉባዔውን በአርባ ምንጭ ፓራዳይዝ ሎጅ አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የምርምር ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክቶሬት 10ኛውን ዓመታዊ የምርምር ግምገማ ዎርክሾፕ ከጥር 19 -20/2015 ዓ.ም አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ የብዝሃ ሕይወት ጥናት ኢንስቲትዩት፣ አሜሪካ ሀገር ከሚገኘው ‹‹Alabaster International››፣ ከኬንያው ጆሞ ኬንያታ የግብርናና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲና ከ‹‹Girl Child Network›› ጋር እንሰትን በኢትዮጵያና በምሥራቅ አፍሪካ ለማስታዋወቅና የምግብ ዋስትና መፍትሔ ለማድረግ የሚያስችል የጋራ ፕሮጀክት ቀርጸው ለመሥራት ቅድመ ዝግጅቶችን እያጠናቀቁ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ተቋማቱ በቅርቡ የመግባቢያ ስምምነት በመፈራረም ወደ ሥራ የሚገቡ ሲሆን ከተቋማቱ የመጡ የሥራ ኃላፊዎች በመስኩ የተሠሩ የምርምር ሥራዎችንና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ከዩኒቨርሲቲው አመራሮችና የዘርፉ ተመራማሪዎች ጋር በመሆን ከጥር 17-19/2015 ዓ/ም የመስክ ምልከታና የጋራ ውይይት አካሂደዋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: እንሰትን በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎችና በምሥራቅ አፍሪካ ለማስተዋወቅ የሚያስችለው የጋራ ፕሮጀክት ቅድመ ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ ነው