
- Details
በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ18ኛ በሀገራችን ለ17ኛ ጊዜ የተከበረው ዓለም አቀፍ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ቀን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለ8ኛ ጊዜ ‹‹በሥነ ምግባር የታነፀ አመራር ከሙስና ለፀዳች ኢትዮጵያ!›› በሚል መሪ ቃል ኅዳር 21/2014 ዓ/ም በተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር ተከብሯል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
በአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በሀገር በቀል 3ኛ ዲግሪ ፕሮግራም በ“Irrigation Engineering”፣ “Ground Water Engineering”፣ “Water Supply and Sanitary Engineering” ለመማር ያመለከታችሁ አመልካቾች እና የመጀመሪያውን ምልመላ ያለፋችሁ አመልካቾች የ“Home-Grown Collaborative PhD Programs (HCPP)” ፕሮጀክት በአሁኑ ጊዜ ባለመኖሩ በዩኒቨርሲቲው መደበኛ የ3ኛ ዲግሪ ፕሮግራም መቀጠል የምትፈልጉ የመጨረሻውን የመግቢያ ፈተና በቀን 30/3/2014 ዓ.ም የሚሰጥ ስለሆነ ፍላጎቱ ያላችሁ ከላይ በተጠቀሰው ቀን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ በአካል በመገኘት እንድትፈተኑ እናሳስባለን፡፡

- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት 10 ሚሊየን ብር እንዲሁም በጦርነቱ ምክንያት ተፈናቅለው ደብረ ብርሃን ከተማ ለተጠለሉ ወገኖች የሚውል አንድ ሚሊየን ብር የሚያወጣ የምግብ እህል ድጋፍ ኅዳር 14/2014 ዓ/ም አድርጓል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለሀገር መከላከያ ሠራዊትና ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ አደረገ

- Details
የዩኒቨርሲቲው “RUNRES” ፕሮጀክት ከመጀመሪያ ዙር ቆይታው የ2 ዓመታት አፈፃፀሙን ለመቃኘት ኅዳር 02/2014 ዓ/ም በኃይሌ ሪዞርት ወርክሾፕ አዘጋጅቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ “RUNRES” ፕሮጀክት የአፈፃፀም ቅኝት ወርክሾፕ አካሄደ
- Details
ከአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች በኢንተርንሺፕ ላይ የቆያችሁ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ መመለሻ ጊዜ ኅዳር 24/2014 ዓ.ም ሲሆን የመመዝገቢያ ጊዜ ከኅዳር 24-26/2014 ዓ.ም መሆኑን እያሳወቀ ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትመለሱ በኢንተርንሺፕ ላያ የቆያችሁበትን ሪፖርት አጠናቅቃችሁ ለሚመለከተው ፋከልቲ ገቢ እንድታደርጉ ዩኒቨርሲቲው በጥብቅ ያሳስባል፡፡
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት