
- Details
የአገሪቱን መረጃና የመረጃ መሠረተ ልማቶች ለመጠበቅ የሚያስችል አቅም በመገንባት የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም የማስጠበቅ ተልዕኮን አንግቦ እየሠራ የሚገኘው የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ /INSA/ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመስኩ የሠለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራት እንዲሁም በምርምርና ልማት ሥራዎች ላይ በትብብር ለመሥራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ የካቲት 10/2014 ዓ/ም ውይይት አካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ /INSA/ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር መሥራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሄደ

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ/ም የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ጥር 27/2014 ዓ/ም የዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት በተገኙበት ተካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል በአርባ ምንጭ ከተማ ከሚገኙ ት/ቤቶች ለተወጣጡ 100 የ7ኛና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ዓባያ ካምፓስና ዋናው ግቢ በሚገኙ ቤተ-ሙከራዎች በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምኅንድስናና ሒሳብ ትምህርት መስኮች ከጥር 28/2014 ዓ/ም ጀምሮ ለ15 ቀናት የሚቆይ የተግባር ሥልጠና እየሰጠ ነው፡፡

- Details
በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ መንግሥት ፍትሕ ቢሮና በክልሉ በሚገኙ 7 ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም በጋራ በተከናወኑ የፍትሕና የሕግ አገልግሎት ሥራዎች አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የላቀ አፈጻጸም በማስመዝገብ የእውቅናና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶለታል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በፍትሕና የሕግ አገልግሎት ሥራዎች የላቀ አፈጻጸም በማስመዝገብ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የእውቅናና የዋንጫ ሽልማት ተበረከተለት