- Details
The University seeks competent, committed and interested Ethiopian academic staff to assign for the Deanship position for college of Agricultural Sciences.
Advertisement for Deanship Position of College of Agricultural Sciences-2013
- Details
በ2012 ዓ/ም ሊሰጥ የነበረው ሀገር አቀፍ የሕግ መውጫ ፈተና (Exit Exam) በኮቪድ-19 መከሰት ምክንያት ወደ 2013 ዓ/ም መተላለፉ ይታወሳል፡፡
ስለሆነም ፈተናው የሚሰጠው ከኅዳር 1-4/2013 ዓ/ም በመሆኑ ፈተናውን መውሰድ የምትፈልጉ በሙሉ ከጥቅምት 2-12/2013 ዓ/ም ድረስ ብቻ ብር 664.00 ( ስድስት መቶ ስልሳ አራት ብር ብቻ) በኤጀንሲው የባንክ ሒሳብ ቁጥር 0171597578400 ገቢ ያደረገባችሁበትን ደረሰኝ በመያዝ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ት/ቤት ቀርባችሁ መመዝገብ እንደምትችሉ እናሳውቃለን፡፡
Read more: በ2013 ዓ/ም የሕግ መውጫ ፈተና (Exit Exam) መፈተን ለምትፈልጉ በሙሉ
- Details
ለድህረ ምረቃ አዲስ አመልካቾች በሙሉ
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ድህረ ምረቃ ት/ቤት ለ2013 ዓ/ም የትምህርት ዘመን በመደበኛ እና በሳምንት መጨረሻ መርሃ ግብር መስፈርቱን የሚያሟሉ አዲስ አመልካቾችን እየመዘገባ መቆየቱ ይታወቃል፡፡
መስከረም 30 ዕለተ ቅዳሜ 2013 ዓ/ም ሊሰጥ የነበረው የድኅረ ምረቃ የመግቢያ ፈተና ፈተናው የሥራ ቀናት ላይ እንዲሆን ከተለያዩ አመልካቾች ጥያቄ በቀረበው መሠረትና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ምክንያት ፈተናው ለ3ኛ ጊዜ ለጥቅምት 09 ዕለተ ሰኞ 2013 ዓ/ም የተዛወረ መሆኑን ከይቅርታ ጋር እንገልፃለን፡፡

- Details
የዩኒቨርሲቲው ካውንስል መስከረም 20/2013 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው የ2013 በጀት ዓመት ዓመታዊ ዕቅድ ላይ ውይይት በማድረግ አፅድቋል፡፡ ለዕቅዱ ማስፈጸሚያ ለመደበኛ እና ለካፒታል በድምሩ ብር 1,594,367,000 ተመድቧል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ