- Details
ለድህረ ምረቃ አዲስ አመልካቾች በሙሉ
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ድህረ ምረቃ ት/ቤት ለ2013 ዓ/ም የትምህርት ዘመን በመደበኛ እና በሳምንት መጨረሻ መርሃ ግብር መስፈርቱን የሚያሟሉ አዲስ አመልካቾችን እየመዘገባ መቆየቱ ይታወቃል፡፡
ትናንት በወጣው የፈተና ጊዜ ማስታወቂያ በ25/01/13 ዓ/ም ሊሰጥ የነበረው የድህረ ምረቃ የመግቢያ ፈተና በአመልካቾች ጥያቄ መሠረት ለ30/01/13 ዓ/ም የተዛወረ መሆኑን እየገለፅን ተፈታኞች በተጠቀሰው ቀን ከጥዋቱ 02፡30 ጀምሮ በየተመደባችሁበት የመፈተኛ አዳራሽ እንድትገኙ እናሳውቃለን፡፡
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ድህረ ምረቃ ት/ቤት ለ2013 ዓ/ም የትምህርት ዘመን በመደበኛ እና በሳምንት መጨረሻ መርሃ ግብር መስፈርቱን የሚያሟሉ አዲስ አመልካቾችን እየመዘገባ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ የምዝገባ ጊዜ የተራዘመ መሆኑን ባሳወቅነው ማስታወቂያ የመግቢያ ፈተና ጊዜ ወደ ፊት እንደሚገለፅ የተነገረ ሲሆን በዚሁ መሠረት ለሁሉም አመልካቾች የመግቢያ ፈተና የሚሰጠው በድህረ ምረቃ ት/ቤት ሕንፃ መስከረም 25/2013 ዓ/ም ከሰዓት ከ08፡00 ጀምሮ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
- Details
UIL & TT Executive Director has planned to undertake the transfer of new technologies and/or adopts the already existing ones to industries/community in 2013 E.C fiscal year.
In line with this, if you have any problem solving idea or technology to be conveyed to our society/industry, submit your proposal until 15 October 2020 to:
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ቦርድ ለዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝደንት ከዩኒቨርሲቲው መምህራን መካከል አወዳድሮ ለመመደብ ይፈልጋል፡፡
የአመልካቾች ትምህርት ደረጃ ሁለተኛ ዲግሪ እና ከዚያ በላይ ሆኖ ከማመልከቻቸው ጋር ቀጥሎ የተዘረዘሩ ማስረጃዎችን በማያያዝ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
Read more: በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝደንትነት ውድድር የወጣ የውስጥ ማስታወቂያ
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የብዝሃ-ሕይወት ምርምርና ጥበቃ ማዕከልና የእንሰትና የመድኃኒት ዕፅዋት ምርምርና ጥበቃ ፓርክ የአካባቢውን ሥነ-ምህዳር በጠበቀ መልኩ የምርምር ሥራዎችን እየከናወነ ነው፡፡
የብዝሃ-ሕይወት ምርምርና ጥበቃ ማዕከል ዳይሬክተርና የሆርቲካልቸር ት/ክፍል ተባባሪ ፕሮፌሰር ሰይፉ ፈቴና የምርምር ማዕከሉ በዋናነት የዘር ምንጭ ሆኖ ለምርምርና ለማስተማሪያነት እያገለገለ የሚገኝ ሲሆን የአካባቢውን ሥነ-ምህዳር በጠበቀ መልኩ የእንሰት ዝሪያዎችን በመንከባከብና በመጠበቅ እንዲሁም በእንሰት ዝሪያዎች ላይ የሚከሰቱ አንዳንድ ችግሮችን በሳይንሳዊ መንገድ ጥናትና ምርምር በማካሄድ በመለየት ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት እየተሠራ ነው፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የብዝሃ-ሕይወት፣ የእንሰትና የመድኃኒት ዕፅዋት ምርምርና ጥበቃ ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸው ተገለፀ
- አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ2013 የት/ዘመን በህክምናና ጤናው ዘርፍ ሁለት የማስተርስ ዲግሪ ፕሮግራሞችን ሊከፍት ነው
- COVID-19 Digital Awareness Program
- አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ‹‹Infectious Diseases›› 3ኛ ዲግሪና በ ‹‹Bio-Medical Sciences›› 2ኛ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራም ሊከፍት ነው
- የቤኔፊት ሪያላይዝ /BENEFIT-REALISE/ ፕሮግራም የሴፍትኔት ተጠቃሚ አርሶ አደሮችን ከተረጂነት ለማውጣት እየሠራ ያለው ሥራ አበረታች መሆኑ ተጠቆመ