የዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት ባካሄዱት የ2008 በጀት ዓመት አንደኛ ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ በሩብ ዓመቱ የታዩ ጠንካራ አፈፃፀሞች፣ ክፍተቶች፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና የተወሰዱ የመፍትሄ እርምጃዎች በሠፊው ተዳሰዋል፡፡ Click here to see the Pictures.

OFAB (Open Forum for Agricultural Biotechnology) አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲን የSouth Node ማዕከል አድርጎ በመምረጥ የምስረታ አውደ ጥናቱን ጥር 07/2008 ዓ.ም አካሂዷል፡፡ Click here to see the Pictures.

የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ማህበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከኮምፒውተር ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ትምህርት ክፍል ጋር በመተባበር ከአርባ ምንጭ ከተማና አካባቢው 2ኛ ደ/መ/ት/ቤቶች ለተወጣጡ 95 መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች ከታህሳስ 23 - ጥር 21/2008 ዓ/ም ለተከታታይ አራት ቅዳሜዎች መሠረታዊ የኮምፒውተር ክህሎት ስልጠና ሰጥቷል፡፡ Click here to see the Pictures.

ከኢትዮጵያ ጤና አጠባበቅ ማኅበር እና ከ CDC/Center for Disease Control and Prevention/ ጋር በመተባበር የሚሠራው የአርባ ምንጭ ሥነ-ህዝብና ጤና ልማት ማዕከል በ2008 ዓ.ም የሀገር ዓቀፉ INDEPTH አባል ሆኗል፡፡

ምርምር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ካስቀመጧቸው የትኩረት መስኮች አንዱና መሰረታዊ እንደመሆኑ መጠን ተቋሙንና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እንዲሁም በገበያ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት የሚያስችል ነው፡፡