በተለያዩ የውሃ ምህንድስና ዘርፍ በሦስተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ለመማር አመልክታችሁ በተለያየ ምክንያት ፈተናው ያመለጣችሁ ተማሪዎች ለመጨረሻ ጊዜ ፈተናው  በቀን 28/01/2012 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

የዩኒቨርሲቲው ቤተ-መጽሐፍትና መረጃ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት በአዲሱ የነጥብ ሥራ ምዘናና ደረጃ አወሳሰን (JEG) በሥሩ በተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለተመደቡና ለነባር 170 ሠራተኞች የቤተ-መጽሐፍት ዓይነቶችና ምንነት፣ አደረጃጀት፣ ህግና ደንብ፣ አገልግሎት አሰጣጥ፣ ደንበኛ አያያዝ፣ የቴክኒክ ክፍሎች እንዲሁም ዲጂታላይዜሽንና አውቶሜሽን፣ ዶክዩሜንቴሽን እና ማጣቀሻ በሚሉ ርዕሶች ላይ ጳጉሜ 4-5/2011 ዓ/ም የሥራ ላይ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ምስሉን ለማየት ከዚህ ይጫኑ

የኢትዮጵያ ህዋ ሣይንስ ማኅበር የበላይ ጠባቂና የእንጦጦ ህዋ ምርምርና ልዩ ማሠልጠኛ ማዕከል የቦርድ ሊቀመንበር አቶ ተፈራ ዋልዋ በጉጌ የህዋ ሣይንስ ምርምር ማዕከል ቅድመ አዋጭነት ጥናት ሂደት ዙሪያ ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች ጋር መስከረም 16/2012 ዓ/ም ውይይት አካሂደዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ሲያካሂድ የነበረው የምርምር ማዕከሉ የቅድመ አዋጭነት ጥናት መጠናቀቁ በውይይቱ ወቅት ተገልጿል፡፡ ምስሉን ለማየት ከዚህ ይጫኑ

የዩኒቨርሲቲው RUNRES ፕሮጀክት ስዊዘርላንድ ከሚገኘው ETH Zurich ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ከመስከረም 13 - 14/ 2012 ዓ/ም ፕሮግራሙን ማስጀመሪያ የምክክር መድረክ በኃይሌ ሪዞርት አካሂዷል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንት ዶ/ር ስምኦን ሽብሩ እንደገለፁት ፕሮጀክቱ በሙዝ እሴት ሰንሰለት ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሠራ ሲሆን ዓላማው ገጠርና ከተማን በምግብ እሴት ሰንሰለት በማገናኘት የአካባቢውን የምግብ ደኅንነትና ልማት ማሻሻልና መጠበቅ፣ የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል እና በምግብ ራስን ለመቻል በሚደረጉ አገራዊ ጥረቶች ላይ የበኩሉንን ድርሻ መወጣት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ምስሉን ለማየት ከዚህ ይጫኑ

To strengthen globalization agenda with regard to its academic, research initiatives, staff development and students’ exchange, AMU has signed 5-yearlong collaborative agreement with India’s reputed Vellore Institute of Technology to mutually reinforce research endeavor and engage in staff and student exchange, informed University-Industry Linkage and Technology Transfer Directorate Director, Dr Tolera Seda.