በኢፌዴሪ የመንግስት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 515/99 እና አዋጁን ለማስፈፀም በወጡት ደንቦችና መመሪያዎች እንዲሁም የሥራ ምዘናና ደረጃ አወሳሰንን አስመልክቶ ከፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ጋር በመተባበር ለሰው ኃብት ልማት ዳይሬክቶሬት ሠራተኞች፣ ለሥራ ክፍል ኃላፊዎችና ቡድን መሪዎች ጳጉሜ 2/2007 ዓ.ም ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ የልማትና የሠላም ሥራዎችን ከከተማ አስተዳደሩና ከአካባቢው ኅብረተሰብ ጋር በቅንጅት ለመሥራት የሚያስችለው ‹የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣ የአካባቢ አስተዳደርና ማኅበረሰብ ትስስር የሠላም ፎረም› ነሐሴ 08/2007 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ተመሥርቷል፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሣይንስ ኮሌጅ በተዘነጉ የሞቃታማ አካባቢ በሽታዎች /Neglected Tropical Diseases/ በሀገሪቱ የመጀመሪያውን የምርምርና ሥልጠና ማዕከል ማቋቋሙን ነሐሴ 02/2007 ዓ.ም ባካሄደው ወርክሾፕ ይፋ አድርጓል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲን ማዕከል ያደረገው የአርባ ምንጭ ሥነ-ህዝብና ጤና ልማት ፕሮግራም ‹‹ጥራት ያለው መረጃ ለተሻለ ጤና ልማት›› በሚል መሪ ቃል የግማሽ ቀን የባለድርሻ አካላት ውይይት ተደረገ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በWHaTeR /Water Harvesting Technologies Revisited / ፕሮጀክት በሰገን ህዝቦች ዞን ኮንሶ ወረዳ ያስገነባውን የያንዳ ፋሮ የጎርፍ መስኖ ቅልበሳ ግንባታ ነሐሴ 01/2007 ዓ.ም አስመርቋል፡፡