
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት በዋናው ግቢ ያስገነባውን የሕጻናት ማቆያ ማዕከል ሥራ ለማስጀመር የማዕከሉን የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት አስመልክቶ ሚያዝያ 7/2017 ለህጻናት ወላጆች ገለጻ (Orientation) ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ሳይንስ ኮሌጅ የማኅበረሰብ ጉድኝትና የኢንደስትሪ ትስስር ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከጋሞ ዞን ለተወጣጡ የእንስሳት ጤና ባለሙያዎች የእንስሳት እግርና አፍ በሽታን (Bovine Foot & Mouth Disease) ሥርጭትና መቆጣጠሪያ ዘዴ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሚያዝያ 2/2017 ዓ.ም ሰጥቷል፡፡ ሥልጠናው በኮሌጁ የተከናወነ የምርምር ሥራን መሠረት አድርጎ የተዘጋጀ ነው፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ከጋሞ ዞንና አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ መዋቅር ለተወጣጡ የእንስሳት ጤና ባለሙያዎች ሥልጠና ተሰጠ

- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የስትራቴጂክ ዕቅድ ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት አስተባባሪነት በተቋቋመ ቡድን ዩኒቨርሲቲው ከትምህርት ሚኒስቴርና በሥሩ ከሚገኙ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ጋር የተፈራረመውን የቁልፍ ተግባራት (KPI) አፈጻጸም ያለበትን ደረጃ ለማወቅ የሚያስችል የውስጥ ሱፐርቪዥን ከመጋቢት 29/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ሳምንት የቆየ የውስጥ ምልከታ ተካሄደ፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: የ‹‹KPI›› ትግበራን አስመልክቶ ለአንድ ሳምንት የቆየ የውስጥ ሱፐርቪዥን ተካሄደ

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች አገልግሎት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ከጸረ ሙስናና ሥነ ምግባር መከታተያ ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ለዩኒቨርሲቲው የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች መልካም ሥነ ምግባር፣ የዲስፕሊን ጥሰቶችና ሊወሰዱ የሚችሉ ቅጣቶችን አስመልክቶ ሚያዝያ 4/2017 ዓ/ም ለዋናው ግቢና ለሳውላ ካምፓስ ተማሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ለዩኒቨርሲቲው የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች በሥነ ምግባር መመሪያና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር ተካሄደ

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ኅብረት የ2017 ዓ/ም የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን የካውንስሉ አባላትና የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት መጋቢት 14/2017 ዓ.ም ግምግሟል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ኅብረት የ2017 ዓ/ም የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ገመገመ