
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ እና በመንግሥት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን ትብብር በግንባታ፣ በምክር አገልግሎት ግዥ፣ በውል አስተዳደርና ንብረት አያያዝ ዙሪያ ከነሐሴ 4-7/2014 ዓ/ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናና የተሞክሮ ልውውጥ መድረክ ተዘጋጅቷል፡፡
የመንግሥት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ወልደአብ ደምሴ የሥልጠናው ዓላማ የተሻሉ ተሞክሮዎችን በማጋራትና ግንዛቤ በማስጨበጥ የግዥ አሠራሮች እንዲሻሻሉ እንዲሁም ባለሙያዎቹ የአመለካከት ለውጥ አምጥተው የራሳቸውን አሻራ ማሳረፍ እንዲችሉ ማስቻል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የግዥ ሥራ ጊዜ የማይሰጥና ውስብስብ በመሆኑ የሚሻሻሉ አዋጆችና የመመሪያ ለውጦችን በማየት ፈጻሚዎች በመተባበር እና ሕግና ሥርዓቱን ተከትሎ በመሥራት ኃላፊነታቸውን መወጣትና ራሳቸውን ማሻሻል እንደሚገባቸው ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በግንባታ፣ በምክር አገልግሎት ግዥ፣ በውል አስተዳደርና ንብረት አያያዝ ዙሪያ ሥልጠና ተሰጠ

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል ከዩኒቨርሲቲው የማኅበረሰብ ጉድኝትና ከተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክቶሬቶች እንዲሁም ከ STEMpower መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር በመተባበር ከጋሞ፣ ጎፋና ኮንሶ ዞኖች እና ከደራሼ፣ ባስኬቶ፣ ቡርጂና አማሮ ልዩ ወረዳዎች ለተወጣጡ 291 ከ7ኛ-12ኛ ክፍል ተማሪዎች በኬሚስትሪ፣ ባዮሎጂ፣ ፊዚክስ፣ ሒሣብ፣ ኤሌክትሮኒክስና ICT ትምህርቶች ከሐምሌ 15 - ነሐሴ 30/2014 ዓ/ም የሚቆይ ሥልጠና እየሰጠ ነው፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል ከ7ኛ-12ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች የክረምት ሥልጠና እየሰጠ ነው

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር ከ15 ዓመት በታች በሁለቱም ፆታዎች የፓይለት ፕሮጀክት ምዘና ውድድር ከሐምሌ 17-ነሐሴ 1/2014 ዓ/ም ለመጀመሪያ ጊዜ በአርባ ምንጭ ከተማ አካሂዷል፡፡

- Details
የ‹‹International Youth Fellowship (IYF)›› ሊቀ መንበርና አስተሳሰብ ቀረጻ አስተምህሮ/Mindset Education/ ስፔሻሊስት የሆኑት ዶ/ር ቾው ሱንግዋ/Dr Cho Sunghwa/ ‹‹Public Lecture on Mindset›› በሚል ርዕስ የተዘጋጀ የሕዝብ ገለጻ/Public lecture/ ሐምሌ 29/2014 ዓ/ም አቅርበዋል፡፡
Read more: ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች አእምሮ ቀረጻ (Mindset) የሕዝብ ገለጻ ቀረበ

- Details
በአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሚቲዎሮሎጂና ሃይድሮሎጂ ፋከልቲ አዘጋጅነት ‹‹Potential Collaborations on Tropical Meteorology and Climate Research Some Ideas on Multi-Disciplinary Approach›› በሚል ርዕስ ሐምሌ 22/2014 ዓ/ም ሴሚናር ተካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በሚቲዎሮሎጂና በአየር ንብረት ምርምር በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ሴሚናር ተካሄደ