
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የማኅበረሰብ ጉድኝት ዳይሬክቶሬት ለሳውላ፣ ጨንቻ፣ ጫኖ ዶርጋ፣ ጻይቴና ጋርዳ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች እና በአርባ ምንጭ ከተማ ለሚገኙ ወጣት ማዕከላት በተለያዩ የትምህርት አይነቶች የተዘጋጁ የማጣቀሻና ልብ ወለድ መጻሕፍትን ሐምሌ 10/2014 ዓ/ም አበርክቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

- Details
በጫሞ ሐይቅ ተፋሰስ ላይ ለመተግበር የታሰበውን የአነስተኛ መሬትና የውሃ አያያዝ ሥራዎች ፕሮጀክት በተመለከተ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች፣ ከኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን እና ከጋሞ ዞን የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ነሐሴ 5/2014 ዓ/ም ወርክሾፕ ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በጫሞ ሐይቅ ተፋሰስ ላይ ለመተግበር በታሰበው የአነስተኛ መሬትና የውሃ አያያዝ ሥራዎች ፕሮጀክት ወርክሾፕ ተካሄደ

- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በብዝሃ ሕይወት ጥበቃና አስተዳደር የ2ኛ ዲግሪ (MSc in Biodiversity Conservation and Management) እና በአካባቢያዊ ሳይንስ የ3ኛ ዲግሪ (PhD in Environmental Science)የትምህርት መርሃ ግብሮች ነሐሴ 9/2014 ዓ/ም የሥርዓተ ትምህርት የውጭ ግምገማ ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በድኅረ ምረቃ የትምህርት መርሃ ግብሮች የሥርዓተ ትምህርት የውጭ ግምገማ አካሄደ

- Details
በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ባዮሎጂ ት/ክፍል በ‹‹Infectious Disease›› የ3ኛ እንዲሁም በ‹‹Medical Entomology and Vector Control›› የ2ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን በ‹‹NORHED-SENUPH II›› ፕሮጀክት ድጋፍ ለሚከታተሉ ተማሪዎች በሞሎኪዩላር ባዮሎጂ ቤተ-ሙከራ የሚገኙ የተለያዩ የ‹‹Polymerase Chain Reaction (PCR)›› ማሽኖችን ለምርምር ሥራዎች በመጠቀም ዙሪያ ለ3 ሳምንታት የቆየ ሥልጠና ከሐምሌ 25/2014 ዓ/ም ጀምሮ ተሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

- Details
ዓለም አቀፍ የጂኦግራፊያዊ መረጃ ሥርዓት (GIS) ሶፍትዌር፣ የዌብ ጂ.አይ.ኤስና የጂኦዳታቤዝ አስተዳደር መተግበሪያዎች አቅራቢ ድርጅት የሆነው ‹‹Environmental Systems Research Institute (ESRI)›› በአሜሪካን ሀገር ሳንዲያጎ-ካሊፎርኒያ ከሐምሌ 01-09/2014 ዓ/ም ባዘጋጀው ዓለም አቀፍ ‹‹ESRI User Conference›› እና ‹‹Education Summit›› ላይ የተገኘው አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ጋር ኢትዮጵያን ወክሎ ለዓለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ግብ ስኬት የሚረዱ መረጃዎችን እንዲያሰባስብ ከስምምነት መደረሱ ተገልጿል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አሜሪካን ሀገር በተዘጋጀው 43ኛው ዓለም አቀፍ ‹‹ESRI User Conference›› ላይ ተሳተፈ