- Details
በ2017 የትምህርት ዘመን አዲስ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተማሪዎች ቅበላ ረቡዕ ታኅሣሥ 2 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ምዝገባ ሐሙስና ዓርብ ታኅሣሥ 3 እና 4 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ትምህርት የሚጀመረው ሰኞ ታኅሣሥ 7 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲሆን ተወስኗል፡፡

- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በማኅበራዊ ሳይንስና ሥነ ሰብ ኮሌጅ በ"Geography and Environmental Studies" ትምህርት ክፍል በ"Environment and Natural Resource Management" ትምህርት ፕሮግራም የ3ኛ ዲግሪ ትምህርቱን ሲከታተል የቆየው የዕጩ ዶ/ር ጀምበር በክረ የመመረቂያ ጽሑፍ ኅዳር 21/2017 ዓ.ም የውጭና የውስጥ ገምጋሚዎች እንዲሁም አማካሪዎች በተገኙበት ቀርቦ ተገምግሟል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኅበራዊ ሳይንስና ሥነ ሰብ ኮሌጅ የእንግሊዝኛ ቋንቋና ሥነ ጽሑፍ ት/ት ክፍል "Improving the Quality of English Language Teaching Through Reflection " በሚል ርእስ በጋሞ ዞን በሚገኙ አራት 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የሚሠራ 1.75 ሚሊየን ብር የተመደበለት ግራንድ የምርምር ፕሮጀክት ኅዳር 21/2017 ዓ/ም ይፋ ተደርጓል፡፡ ፕሮጀክቱ በከምባ ፣ ጨንቻ ፣ ምዕራብ ዓባያና ሰላምበር 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተግባራዊ የሚሆን ነው፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የእንግሊዝኛ ቋንቋ ማስተማር ጥራትን ለማሻሻል የሚያስችል 1.75 ሚሊየን ብር የተመደበለት ግራንድ ፕሮጀክት ይፋ ሆነ

- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ የተሠራው የሕጻናት ማቆያ ማዕከል የምረቃና ሥራ ማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት ኅዳር 20/2017 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደርና ልማት ጉዳዮች ም/ፕሬዝደንት ጽ/ቤት በሥሩ ከሚገኙ አዲስና ነባር ሥራ አስፈጻሚዎች ጋር ኅዳር 20/2017 ዓ/ም ውይይት ያካሄደ ሲሆን በዕለቱ የ2017 ዓ/ም ዕቅድ የውል ስምምነትም ከሥራ አስፈጻሚዎቹ ጋር ተፈራርሟል።ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የአስተዳደርና ልማት ም/ፕሬዝደንት ጽ/ቤት በሥሩ ከሚገኙ የሥራ ክፍል ኃላፊዎች ጋር ተወያየ