ዩኒቨርሲቲው ከዩናይትድና ከብራይት ኮንስትራክሽን ድርጅቶች ጋር የ2ኛ ዙር የሳውላ ካምፓስ የግንባታ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ውል ሰኔ 28/2008 ዓ.ም ተፈራርሟል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ከህግ ት/ቤት ጋር በመተባበር በደቡብ ኦሞ ዞን ለሚገኙ የማረሚያ ቤት ኃላፊዎችና ሠራተኞች በመሰረታዊ የታራሚዎች መብትና አያያዝ ሰኔ 10/2008 ዓ.ም የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጥቷል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ህብረት የ2008 ዓ/ም የበጀትና ዕቅድ አፈፃፀምን አስመልክቶ ሰኔ 12/2008 ዓ/ም ግምገማ አካሂዷል፡፡ የተማሪዎች ህብረት ተተኪ ሥራ አስፈፃሚ አባላት ምርጫም ተከናውኗል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ የደቡብ ሱዳን ሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች በጋምቤላ ክልል ኑዌር እና አኝዋክ ዞኖች በሚገኙ 13 ቀበሌያት ንፁሃን ዜጎቻችን ላይ የፈፀሙትን አሰቃቂ ግድያና ዝርፍያ በማውገዝ ሚያዝያ 17/2008 ዓ/ም የህሊና ፀሎትና የጧፍ ማብራት ሥነ-ሥርዓት አከናውኗል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

‹‹ትውፊታዊ ዕውቀት፣ የባህል ብዝሃነትና ቅርስ አስተዳደር በኢትዮጵያ›› አራተኛው ሀገራዊ አውደ ጥናት ሰኔ 14/2008 ዓ/ም በማህበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብ ኮሌጅ አዘጋጅነት ተከናውኗል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡