በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በምርምር ማስተባበሪያ ጽ/ቤት አዘጋጅነት ከተለያዩ የትምህርት ክፍሎች ለተወጣጡ የኮሌጁ መምህራንና ተመራማሪዎች ከጥር 23 - 26 ለአራት ተከታታይ ቀናት የጂአይኤስ አጠቃቀም ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ቅርስ ጥበቃ ባለሥልጣንና ከጋሞ ዞን ቱሪዝም መምሪያ ጋር በመተባበር “የጋሞ ዱቡሻ እና የዱቡሻ ዎጋ˝ ሥርዓት የጥናትና ምርምር ማስጀመሪያ የማኅበረሰብ ንቅናቄ መድረክ ጥር 25/20/16 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ት/ቤት የአምሳለ ፍርድ ቤት ፍጻሜ ውድድር ጥር 23/2016 ዓ/ም ያካሄደ ሲሆን ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ውድድር ኢትዮጵያንና አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲን በመወከል በታንዛንያ አሩሻ በተደረገው ጠቅላላ የአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ውድድር ተሳትፈው ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ዕውቅና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ለጳውሎስ ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የፎረንሲክ ሜዲስንና ቶክሲኮሎጂ ስፔሻሊቲ ተማሪዎች ከታኅሣሥ 18 - ጥር 24/2016 ዓ/ም በሁለት ዙሮች የፎረንሲክ ናሙና ምርመራ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ በኢኮኖሚክስ ት/ክፍል በ“Development Economics” ትምህርት ፕሮግራም የ3 ዲግሪ ተማሪ ዕጩ ዶ/ር ሰለሞን ከበደ  የካቲት 01/2016 ዓ/ም ከጧቱ 2፡30 ጀምሮ  የ3 ዲግሪ ማጠናቀቂያ ምርምር ሥራውን የውጪና የውስጥ ገምጋሚዎችና አማካሪዎች በተገኙበት በዋናው ግቢ መግቢያ ላይ በሚገኘው አዳራሽ ያቀርባል፡፡