
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት በደንበኛ አያያዝ፣ ፈጣን አገልግሎት አሰጣጥ እንዲሁም አመራርነት ክሂሎት ዙሪያ ከ5ቱም ካምፓሶች ለተወጣጡ ሴት መምህራን፣ የአስተዳደር ሠራተኞችና አመራሮች ከየካቲት 9-10/2015 ዓ/ም ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

- Details
የአርባ ምንጭ ውኃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ከአሜሪካው ቴክሳስ ግብርናና ሜካኒካል ዩኒቨርሲቲ/ Texsas Agricultural & Mechanical University/ ጋር በመተባባር ‹‹Integrated Decision Support System (IDSS)›› በሚል ርዕስ ከጎረቤት ሀገራት ለመጡና ከሀገር ውስጥ ለተወጣጡ በውኃ ምኅንድስና፣ ግብርና፣ ኢኮኖሚክስ፣ አካባቢ ጥበቃና ሌሎች ዘርፎች የሚያስተምሩ መምህራንና ባለሙያዎች ከጥር 6-10/2015 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ‹‹Integrated Decision Support System›› በሚል ርዕስ ሥልጠና ተሰጠ

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የታዳሽ ኃይል ቴክኖሎጂ ምርምር ማዕከል ከሳሃይ ሶላር አሶሴሽን/Sahay Solar Association/ ጋር በመተባበር ከስዊዘርላንድ፣ ከጋሞና ጎፋ ዞኖች እንዲሁም ከዩኒቨርሲቲው ለተወጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎችና ተማሪዎች የፀሐይ ኃይልን ለመብራትና ለተለያየ አገልግሎት መጠቀም በሚያስችሉ ዘዴዎች /Photovoltaic Technology/ ዙሪያ ከጥር 30 - የካቲት 9/2015 ዓ/ም ለተከታታይ 9 ቀናት የአቅም ግንባታ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

- Details
በ2015 የትምህርት ዘመን አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ቅበላ ቀን የካቲት 22/2015 ዓ/ም፣ የምዝገባ ቀን የካቲት 23 እና 24 ቀን 2015 ዓ.ም ፣ ትምህርት የሚጀመርበት ቀን የካቲት 27 ቀን 2015 ዓ.ም እንዲሆን ተወስኗል፡፡
ስለሆነም ተማሪዎች በተጠቀሰው ቀን ወደ ዩኒቨርሲቲው በሚትመጡበት ጊዜ፡-

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ ጉድኝት ዳይሬክቶሬት በጨንቻ ዙሪያ ወረዳ በሚገኘው ሻማ ጎማ፣ ቀርጴ እና በሌ ቀርጴ መንደሮች ላይ በ1.9 ሚሊየን ብር ያስገነባውን የሻማ ቀበሌ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የካቲት 12/2015 ዓ/ም አስመርቋል፡፡ ከፕሮጀክት ሥራው 400 ሺህ ብር ወጪ የተሸፈነው ማኅበረሰቡ በጉልበቱ ባበረከተው አስተዋፅዖ ነው፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ1.9 ሚልየን ብር ያስገነባውን የሻማ ቀበሌ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት አስመረቀ