- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሙያ ማበልጸጊያ ማዕከል የደረጃ ዶት ኮም እህት ኩባንያ/Dereja.Com Sister Company/ ከሆነው ኢንፎማይንድ ሶሉሽንስ “Infomind Solutions” እና ከጋሞ ዞን የሥራ ዕድል ፈጠራ ቢሮ ጋር በመተባበር ከአርባ ምንጭ ከተማ እና ከጋሞ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች ለተወጣጡና ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች አዲስ ለተመረቁ ወጣቶች በ “Dereja Academy Accelerator Program”̋ ክሂሎት ላይ ያተኮረ ሥልጠና ከነሐሴ 26/2015 ዓ/ም ጀምሮ ለተከታታይ ሦስት ወራት እየሰጠ ይገኛል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: በጋሞ ዞን ለሚገኙ ወጣቶች በ“Dereja Acadamy Accelerator Program” ላይ ያተኮረ ሥልጠና እየተሰጠ ነው
- Details
Arba Minch University has offered the British Council-funded hybrid training of trainers on Instructional English for Secondary School Teachers and Project Proposal Writing for Grants for Instructors of English Language and Literature, Ph.D. candidates, and Masters Students in the field, from October 2-3, 2023. Click here to see more photos.
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለድኅረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት የተመዘገባችሁ እንዲሁም ትምህርት ሚኒስቴር በገለጸው መሠረት ለድኅረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (GAT) ያልተመዘገባችሁና የልምምድ ፈተናውን (Mock Exam) ያልወሰዳችሁ አመልካቾች የምዝገባና የልምምድ ፈተና መውሰጃ የመጨረሻ ቀን ነገ መስከረም 25/2016 ዓ/ም ብቻ ስለሆነ ከወዲሁ ዕድሉን እንድትጠቀሙበት ዩኒቨርሲቲው እያሳሰበ ለመመዝገብ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቴሌ ብር ሱፐርአፕ https://portal.aau.edu.et ወይም ለዚህ ፈተና ብቻ በሚያገለግለው https://gat.aau.edu.et መጠቀም የምትችሉ መሆኑን ይገልጻል፡፡






