• SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning
  • AMU
    • About AMU
    • Presidents Message
    • Campus Guide
    • Contact us
  • Administration
    • Presidents' Office
      • AMU President
      • Academic Affairs
      • Research and Community Service
      • Administration
  • Directorates
  • Academics
    • School of Graduate Studies
    • Institutes
      • Arba Minch Institute of Technology
      • Arba Minch Water Technology
    • Colleges
      • Agriculture
      • Business & Economics
      • Medicine and Health Sciences
      • Natural & Computational Sciences
      • Social Sciences & Humanities
      • Continuing & Distance Education
      • Sawla Campus
    • Schools
      • School of Law
      • School of Pedagogical and Behavioral Sciences
      • School of Medicine
    • Sport Academy
  • Research
  • Registrar
    • About Us
    • Alumni Registration
    • Alumni
  • Partnership
    • Our Partners
      • International Partners
      • Local Partners
    • Ongoing Projects
    • Completed Projectss
      • Recently Completed
      • Past Projects
    • GCPM Online Forms
  • Journals
    • OMOIJS Journal
    • EJBSS Journal
    • EJWST Journal
    • AMUJCLS Journal
    • EIJET journal
  • Symposia
    • Enset Symposium
    • Enset Symposium 2024

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በኮንሶ ወረዳ ያስገነባውን የ ‘ያንዳ ፋሮ ’ የጎርፍ መስኖ ቅልበሳ ፕሮጀክት አስመረቀ

Details
Wed, 12 August 2015 9:00 pm

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በWHaTeR /Water Harvesting Technologies Revisited / ፕሮጀክት በሰገን ህዝቦች ዞን ኮንሶ ወረዳ ያስገነባውን የያንዳ ፋሮ የጎርፍ መስኖ ቅልበሳ ግንባታ ነሐሴ 01/2007 ዓ.ም አስመርቋል፡፡

Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በኮንሶ ወረዳ ያስገነባውን የ ‘ያንዳ ፋሮ ’ የጎርፍ መስኖ ቅልበሳ ፕሮጀክት አስመረቀ

በህፃናት ህገ-ወጥ ዝውውር እና ጉልበት ብዝበዛ ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት ተካሄደ

Details
Mon, 03 August 2015 5:15 am

በዩኒቨርሲቲው የሶስዮሎጂና ሶሻል አንትሮፖሎጂ ትምህርት ክፍል እና በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ ሴቶች ፣ ህፃናትና ወጣቶች ቢሮ ትብብር የህፃናት ህገ-ወጥ ዝውውርና ጉልበት ብዝበዛ ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት ከተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች የመጡ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ሐምሌ 9/2007 ዓ.ም ተካሄደ ፡፡ Click here to see the Pictures.

Read more: በህፃናት ህገ-ወጥ ዝውውር እና ጉልበት ብዝበዛ ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት ተካሄደ

ለሒሳብ ትምህርት ክፍል መምህራንና የድህረ- ምረቃ ተማሪዎች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጠ

Details
Thu, 30 July 2015 9:00 pm

በተፈጥሮ ሳይንስ ኮሌጅ የሒሳብ መምህራንና የድህረ -ምረቃ ተማሪዎች ለሚያደርጉት ጥናትና ምርምር የተሻለ አቅም ለመፍጠርና የሒሳብ ትምህርት በሳይንሱ ዘርፍ ጉልህ ሚና እንዲኖረዉ ለማስቻል   <<The Role of Mathematics Now and in the Futuer>>በሚል ርዕስ ሐምሌ 11/2007 ዓ.ም ስልጠና ተሰጥቷል ፡፡
በዕለቱ በሳይንስ ትምህርት ላይ ያተኮሩ ሶስት የተለያዩ ጥናታዊ ጽሁፎች የቀረቡ ሲሆን ስልጠናው የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን በሒሳብ ትምህርት ለጥሩ ውጤት ለማብቃት የሚያስችሉ የማስተማሪያ ዘዴዎች ፣ የፈተና ዝግጅት እና  የጥናታዊ ጽሁፍ ስነ-ዘዴዎች ላይ ያተኮረ ነበር  ፡፡ በቀጣይም የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመቀናጀትና በመደጋገፍ መስራት  እንዳለባቸው በስልጠናዉ ወቅት ተጠቁሟል ፡፡   
በአሁኑ ጊዜ በሒሳብ ትምህርት ዘርፍ የሚደረጉ ጥናትና ምርምሮች  አናሳ በመሆናቸዉና  በሌሎች የሳይንስ ትምህርቶች እየተዋጠ ስለሆነ የትምህርት ክፍሉ  ተጠናክሮ  የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በመቅረፅና ጥናትና ምርምሮች በመስራት ችግሩን መቅረፍ  እንደሚገባው  የትምህርት ክፍሉ መ/ር ገብረፃድቅ ግደይ ገልፀዋል ፡፡
በፕሮግራሙ USA ከሚገኘው ሮዋን ዩኒቨርሲቲና  ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ የመጡ  የተለያዩ የጥናትና ምርምር አቅራቢዎች፣ የተፈጥሮ ሳይንስ ኮሌጅ የሒሳብ ትምህርት ክፍል  መምህራን እንዲሁም  ከትምህርት ሚኒስቴር ተመድበዉ የመጡ 110  የድህረ-ምረቃ የክረምት ተማሪዎች ተገኝተዋል፡፡

15ኛው ዘላቂ የውሃ ሀብት አስተዳደርና አጠቃቀም ሲምፖዚዬም ተካሄደ

Details
Thu, 23 July 2015 11:19 am

በዩኒቨርሲቲው ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የምርምር ዳይሬክቶሬትና በውሃ ሀብት ምርምር ማዕከል ዳይሬክቶሬት ትብብር 15ኛው ዘላቂ የውሃ ሀብት አስተዳደርና አጠቃቀም ሲምፖዚዬም ከሰኔ 26 እስከ 27/2007 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡

ሲምፖዚዬሙ በዘላቂ የውሃ ሃብት አስተዳደርና አጠቃቀም ዙሪያ ባለሙያዎች፣ ተመራማሪዎች እና ባለድርሻ አካላት የጋራ መድረክ በመፍጠር የምርምር ውጤቶችን እንዲያቀርቡና የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን እንዲለዋወጡ ለማድረግ ያለመ መሆኑን በዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂ ኢንሲትቲዩት የውሃ ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ዶ/ር መኮንን አያና ተናግረዋል፡፡ ለአገር ልማት አስተዋጽኦ ሊያደርጉ የሚችሉ በርካታ የጥናትና ምርምር ውጤቶች የሚቀርቡበት መድረክ በመሆኑ በውሃ ሃብት ዙሪያ ለፖሊሲ አውጭዎች ግብዓት ሊሆን የሚችል መሆኑንም አስገንዝበዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ፈለቀ ወልደየስ በመክፈቻ ንግግራቸው ኢትዮጵያ በውሃ ሀብት ያላትን ከፍተኛ አቅም በአግባቡ ለመጠቀም እንዳትችል በመስኩ የሚታየው የባለሙያና የፋይናንስ አቅም ውስንነት ድርሻው የጎላ ነው ብለዋል፡፡የውሃ ሀብት አስተዳደርና አጠቃቀም በሳይንሳዊ የጥናትና ምርምር ሥራዎች መደገፍ እንደሚገባው የገለፁት ፕሬዝዳንቱ ዩኒቨርሲቲው በግንባር ቀደምነት ባለሙያዎችን በማሰልጠን በዘርፉ የሚታየውን ውስንነት ለመቅረፍ የራሱን አስተዋጽኦ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡

በኢፌዴሪ የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የምርምር ዳይሬክተር አቶ አቢቲ ጌታነህ በመስኖ ልማት ፕሮጀክት፣በሰው ኃይል ስልጠና፣ በምርምር እና በሌሎችም ተያያዥ ዘርፎች በሚኒስቴር መ/ቤቱ በኩል የታቀዱ ሥራዎችንና የዩኒቨርሲቲዎችን ሚና አስመልክተው ለተሳታፊዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በመጀመሪያው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ዘመን በመስኖ ልማት ሀገራችን ካላት አቅም ከ40-50 በመቶ መጠቀም የተቻለ ሲሆን በኤሌክትሪክ ኃይል ከውሃ ፣ ከነፋስና ከጂኦተርማል ኃይል እንዳላት ከሚገመተው 45 ሺ ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም 10ሺ የሚሆነውን ለማሳካት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡ በሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ዘመን በዘርፉ ባለሙያዎችን በብዛትና በጥራት በማፍራትና በጥናትና ምርምር የተሻለ ሥራ እንደሚሠሩ ጠቁመዋል፡፡

በሲምፖዚዬሙ ከተለያዩ ተቋማት በመጡ ባለሙያዎችና ተመራማሪዎች 62 የጥናትና ምርምር ጽሑፎች ተመርጠው 28ቱ በመድረክና 11 ጥናቶች በፖስተር ቀርበዋል፡፡ በተጨማሪም ኔዘርላንድ ከሚገኘው ዋግናይን ዩኒቨርሲቲ የመጡትና በውሃ ሃብት ዘርፍ የረጅም ጊዜ ልምድ ያላቸው ፕሮፌሰር ሄንክ ሪትማን ‹‹በፍሳሽ አወጋገድ ዙሪያ የተዘነጉ እውነታዎች ›› በሚል ርዕስ ያቀረቡት ጥናታዊ ጽሑፍ የፍሳሽ አወጋገድ ምንነት፣ ዓላማና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን ዳሷል፡፡

በሲምፖዚዬሙ የዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መምህራንና ኃላፊዎች፣ ዳይሬክተሮች፣ ከውሃ ሀብት ሚኒስቴር፣ ከተለያዩ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችና አጋር ተቋማት በአጠቃላይ 120 ተሳታፊዎች ተገኝተዋል፡፡ በማጠቃለያው የጥናትና ምርምር ጽሑፍ ላቀረቡ ባለሙያዎችና ለሲምፖዚዬሙ ስኬት ጉልህ ድርሻ ለነበራቸው አካላት በዩኒቨርሲቲው የምርምርና ማህበረሰብ አገ/ም/ፕሬዝዳንት አማካኝነት የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል፡፡



በቴክኖሎጂ ፈጠራ፣ ማላመድና ሽግግር ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጠ

Details
Thu, 23 July 2015 11:18 am

የዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂ ሽግግር ማስተባበሪያና ኮሜርሻላይዜሽን ጽ/ቤት ከኢትዮጵያ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በቴክኖሎጂ ፈጠራ፣ ማላመድና ሽግግር ዙሪያ ከግንቦት 27-28/07 ዓ/ም የሁለት ቀናት ስልጠና ሰጥቷል፡፡

ሥልጠናው ለዩኒቨርሲቲውና ለአካባቢው ማህበረሰብ በቴክኖሎጂ ፈጠራ፣ ማላመድና ሽግግር እንዲሁም በአእምሯዊ ንብረት አጠባበቅ ዙሪያ ግንዛቤ ለማስጨበጥ የተዘጋጀ መሆኑን የማስተባበሪያ ጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ አሰፋ ደሴ ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ አእምሯዊ ሀብት ጽ/ቤት ባለሙያ አቶ ፈቃዱ ኃይሌ በስልጠናው ላይ እንደተናገሩት ሚኒስቴር መ/ቤቱ በህብረተሰቡ ዘንድ የአእምሯዊ ንብረት እውቀት እንዲዳብርና በቂ የህግ ጥበቃ እንዲያገኝ በመሥራት ላይ ነው፡፡

አዳዲስ ነገሮችን የመፍጠር፣ የማላመድና የማሸጋገር ሥራዎችን በማጠናከር ለማህበረሰቡ ችግር አማራጭ መፍትሄ ለመስጠት በሚቻልበት ሂደትና የፈጠራው ባለቤቶች ከውጤቱ መጠቀም እንዲችሉ እየሰራ መሆኑን በሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስተር የቴክኖሎጂ ሽግግርና ልማት ዳይሬክቶሬት ባለሙያ አቶ ተረፈ ቤኛ ገልፀዋል፡፡ ይህም በሚኒስቴር መ/ቤቱ ሀገራዊ አቅጣጫዎችን በተከተለ መንገድ ልማቱን የሚያፋጥኑ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎች ወደ ተግባር እንዲለወጡ የማድረግ ሥራዎች በማከናወን ላይ እንደሚገኙም ነው አቶ ተረፈ የተናገሩት፡፡

በዩኒቨርሲቲው የምርምርና የማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጉቼ ጉሌ በስልጠናው መክፈቻ ባደረጉት ንግግር ዩኒቨርሲቲው በምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ሊያደርጉ የሚችሉ በርካታ ሥራዎችን በቴክኖሎጂ ፈጠራ፣ማላመድና ሽግግር ላይ በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡ከዚህም ጎን ለጎን በጥቃቅንና አነስተኛ ዘርፎች ላይ የተደራጁና መሰል ሥራዎችን በማከናወን ላይ ያሉ የማህበረሰብ ክፍሎችን አቅም ከማጎልበት አንጻር የተሻለ ግንዛቤ ለመፍጠር ግብዓት የሚሆን ስልጠና ለማዘጋጀት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ዶ/ር ጉቼ ተናግረዋል ፡፡

በዩኒቨርሲቲው የማህ/አገ/ዳ/ጽ/ቤት ሥር የሚገኘው ቴክኖሎጂ ሽግግርና ኮሜርሻላይዜሽን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ከሚሰሩ አዳዲስ የምርምር ሥራዎች ውስጥ ለማህበረሰቡ የሚጠቅሙትን በመምረጥ፣ በመገምገምና ወደ ተግባር እንዲለወጡ በማበረታታት ተቀባይነት ያገኙትን በኢትዮጵያ አእምሯዊ ሀብት ጽ/ቤት ዕውቅና እንዲሰጣቸው ያመቻቻል፡፡

በሥልጠናው በአርባ ምንጭ ከተማ ከተደራጁ ጥቃቅንና አነስተኛ ማኅበራት፣ የፈጠራ ሥራ ባለቤቶችና በዩኒቨርሲቲው ከተለያዩ የትምህርት ክፍሎች የተወጣጡ መምህራንና ተመራማሪዎች የተሳተፉ ሲሆን በቀጣይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን የማላመድና የማሸጋገር ሥራዎችን በትብብር እንደሚሰራ የማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር አለማዬሁ ታዬ ገልፀዋል፡፡

  1. በወቅታዊ የሲቪል ምህንድስና ሥራ ልምዶች ላይ ያተኮረ ሲምፖዚዬም ተካሄደ
  2. ለዩኒቨርሲቲው ሴት መምህራን የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ተሰጠ
  3. የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አራተኛ አመት ክብረ በአል በድምቀት ተከበረ
  4. ለዩኒቨርሲቲው የበላይ አመራር በኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ሜይንስትሪሚንግ ላይ ስልጠና ተሰጠ

Page 459 of 523

  • 454
  • 455
  • 456
  • 457
  • 458
  • 459
  • 460
  • 461
  • 462
  • 463

Downloads

  • Newsletter
  • Registrar
  • Academic Calendar
  • Finance & Budget Transparency

Quick Links

  • News
  • Vacancies
  • AMU Intranet
  • ICT Center

Systems

  • SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning
  • Facebook
  • X
  • Telegram
  • Youtube
  • Email

Contact us

Corporate Communication
P.O. Box 21
Arba Minch University

Tel: +251-46881-4986
Fax: +251-46881-0820/0279
E-mail: corcom@amu.edu.et , ictc@amu.edu.et

Registrar

  • About Us
  • Alumni
  • Alumni Registration
  • Contact us

Colleges

  • Agriculture
  • Business & Economics
  • Medicine and Health Sciences
  • Natural Sciences
  • Social Sciences & Humanities

Systems

  • SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning

Copyright © 2025 Arba Minch University. 

  • Campus Guide
  • Contact Us
  • Sitemap