• SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning
  • AMU
    • About AMU
    • Presidents Message
    • Campus Guide
    • Contact us
  • Administration
    • Presidents' Office
      • AMU President
      • Academic Affairs
      • Research and Community Service
      • Administration
  • Directorates
  • Academics
    • School of Graduate Studies
    • Institutes
      • Arba Minch Institute of Technology
      • Arba Minch Water Technology
    • Colleges
      • Agriculture
      • Business & Economics
      • Medicine and Health Sciences
      • Natural & Computational Sciences
      • Social Sciences & Humanities
      • Continuing & Distance Education
      • Sawla Campus
    • Schools
      • School of Law
      • School of Pedagogical and Behavioral Sciences
      • School of Medicine
    • Sport Academy
  • Research
  • Registrar
    • About Us
    • Alumni Registration
    • Alumni
  • Partnership
    • Our Partners
      • International Partners
      • Local Partners
    • Ongoing Projects
    • Completed Projectss
      • Recently Completed
      • Past Projects
    • GCPM Online Forms
  • Journals
    • OMOIJS Journal
    • EJBSS Journal
    • EJWST Journal
    • AMUJCLS Journal
    • EIJET journal
  • Symposia
    • Enset Symposium
    • Enset Symposium 2024

የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ የ‘ISIS’ን የሽብር ጥቃት በጥብቅ አወገዘ

Details
Thu, 23 July 2015 11:04 am

የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ሚያዝያ 16/2007 ዓ.ም በሁሉም ካምፓሶች በተደረገው የጧፍ ማብራት ሥነ-ሥርዓት ላይ በመገኘት በሊቢያ በ30 ኢትዮጵያውያን ላይ ISIS በተባለ አሸባሪ ቡድን እንዲሁም በደቡብ አፍሪካ በ4 ኢትዮጵያውያን ላይ የተፈፀመውን ኢ-ሰብዓዊ ግድያ በጥብቅ አውግዟል፡፡

በዋናው ግቢ በህሊና ፀሎት የተጀመረውን ሥነ-ሥርዓት በከፈቱበት ወቅት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ፈለቀ ወልደየስ እንደተናገሩት በሁለቱም ሀገራት በዜጎቻችን ላይ የተፈፀመው ኢ-ሰብዓዊና አሰቃቂ ግድያ የኢትዮጵያውያንን ልብ በሐዘን የሰበረና በከፍተኛ ሁኔታ ቁጣ የቀሰቀሰ ነው፡፡ ፕሬዝደንቱ የጥቃቱ ሰለባ ለሆኑት ወገኖች የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን በመግለጽ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለመላው ኢትዮጵያውያን መፅናናትን ተመኝተዋል፡፡ በተጨማሪም ሀገራችን ኢትዮጵያ የምታደርገው የዴሞክራሲ ግንባታና ልማት ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሸባሪዎች ዕኩይ ዓላማቸውን ለመፈፀም በሚያቀርቡት ሃይማኖታዊ ሽፋን ሳንደናገር የፀረ ሽብርተኝነት አቋማችን ምንግዜም የፀና መሆኑን ማረጋገጥ እንደሚጠበቅብን አሳስበዋል፡፡

በሌሎቹም ግቢዎች የፕሬዝደንት ተወካዮች፣ የኮሌጅ ዲኖችና የተማሪዎች ኅብረት ፕሬዝደንት ተወካዮች ለተጎጂ ወገኖች የተሰማቸውን ሐዘን በመግለጽ መንግሥት ሽብርተኝነትን ለመከላከል በሚያደርገው እንቅስቃሴ ሁሉም ዜጋ ከጎን በመሆን የሚጠበቅበትን አስተዋፅኦ እንዲያበረክት ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡

በተለይም የተማሪዎች ኅብረት ፕሬዝደንትና ተወካዮቹ በሀገራችን ሠርተን የመሻሻል አማራጮች በርካታ ስለሆኑ በህገ ወጥ መንገድ ከሀገር በመውጣት የአሸባሪዎች ሲሣይ መሆን ሊያበቃ ይገባል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም ሽብርተኝነትን ከመታገል ጎን ለጎን ወጣቶች በሀገር ውስጥ የተፈጠሩና እየተፈጠሩ ያሉ የሥራ አማራጮችን አሟጠው እንዲጠቀሙና በህገ ወጥ መንገድ ከሀገር እንዳይወጡ ግንዛቤ ከማስጨበጥ አንፃር የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ግንባር ቀደም ሚና መጫወት እደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡

በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሽብር ድርጊቱን የሚያወግዙ የተለያዩ የሥነ-ጽሑፍ ዝግጅቶች ቀርበዋል፡፡ የሥነ-ሥርዓቱ ተካፋዮችም ‹‹አክራሪነትና ሽብርተኝነት የትኛውንም ኃይማኖት አይወክልም››፣ ‹‹አንድነታችንን አጠናክረን ሽብርተኝነትን እንዋጋለን››፣ ‹‹የአይኤስአይኤስ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊትን በጥብቅ እናወግዛለን›› የሚሉና ሌሎች መፈክሮችን በመያዝና በጋራ ድምጽ በማሰማት ጧፍ እያበሩ በየግቢው በተዘጋጁ ቦታዎች የጥቃቱ ሰለባዎችን በማሰብ የእግር ጉዞ አድርገዋል::

ዩኒቨርሲቲ አቀፍ የትምህርት ጥራትና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ማጎልበቻ ፎረም ውይይት ተካሄደ፡፡

Details
Thu, 23 July 2015 11:03 am

የፎረሙ ውይይት በዋናው ግቢ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ ዳይሬክተሮች፣ የኮሌጅ ዲኖች፣የአስተዳደር ሠራተኞች፣ መምህራንና ተማሪዎች በተገኙበት ሚያዝያ 30 ተካሂዷል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ፈለቀ ወልደየስ ኮንፈረንሱን በንግግር በከፈቱበት ወቅት መልካም አስተዳደርን ለማስፈንና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ትግል የትምህርት ጥራትና የመልካም አስተዳደር ፎረም ፋይዳው ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም የፎረሙ ተሳታፊዎች ከመልካም አስተዳደርና ከትምህርት ጥራት አንፃር መሻሻል የሚገባቸውን አፈጻጻሞች በተመለከተ የጋራ ግንዛቤ ለመያዝ በሚያስችል መልኩ ውይይቱን እንዲያካሂዱ አሳስበዋል፡፡

ኮንፈረንሱ በዩኒቨርሲቲው ቀደም ሲል በትምህርት ክፍሎችና በኮሌጆች ደረጃ በተከታታይ በተደረጉ ውይይቶች ተለይተው የወጡ ችግሮችንና ድክመቶችን እንደየባህሪያቸው የአጭር፣ የመካካለኛ እና የረዥም ጊዜ ዕቅድ በማውጣት በዘላቂነት ለመፍታት እየተደረጉ ያሉ እንቅስቃሴዎችን አስመልክቶ የአስተዳደር ጉዳዮች ም/ፕሬዝደንት ዶ/ር የቻለ ከበደ የሁሉንም ኮሌጆችና የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሪፖርት አቅርበዋል፡፡

ሪፖርቱን ተከትሎ የሁሉም ኮሌጆች ተማሪዎች፣ መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች አስተያየቶችን፣ ጥቆማዎችንና ጥያቄዎችን በመሰንዘር የመብራት፣ የኢንተርኔት፣ የውሃና ሌሎች ተያያዥ አገልግሎቶች አካባቢ የሚታዩትን ክፍተቶችና ከፍተኛ መሻሻሎች ገምግመዋል፡፡

ዲኖቹ ለአስተያየትና ጥቆማ ሰጪዎች ምስጋና በመቸር ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ በሠጡበት ወቅት የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል መምህራን የትምህርት ክፍለ ጊዜዎችን በአግባቡ እንዲጠቀሙ መደረጉን፣ የብቃት ችግር አለባቸው የተባሉ የአንዳንድ የውጭ አገር መምህራን ኮንትራት መቋረጡን እንዲሁም መምህራን የተማሪዎችን ፈተና በወቅቱ አርመው ውጤታቸውን የሚያሳዩበት ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠር ከትምህርት ክፍሎች ጋር በመተባበር እየተሠራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡ የ1 ለ 5 አደረጃጀት በሁሉም ክፍሎች ውጤታማ ሥራ እንዲያከናውን የሚያስችልና ክትትል የሚያደርግ ከአስተዳደር ሰራተኞች፣ ከመምህራንና ከተማሪዎች የተወከለ የሱፐርቪዢን ቡድን ተቋቁሞ ሥራ ላይ መሆኑንም አሳውቀዋል፡፡

የሁሉም ኮሌጆች ዲኖች እንደተናገሩት ከተማሪዎችና መምህራን እንዲሁም ከአስተዳደር ሠራተኞች የስኬት ማነቆ ሆነው የተለዩትን ችግሮች ለመቅረፍ በተቀመጠው መርሃ ግብር መሠረት እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ናቸው፡፡ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሳደግ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልፀው በቀጣይ በመካከለኛና በረዥም ጊዜ ሊፈቱ የታቀዱ ችግሮችን በተቀናጀ ጥረት ለመሻገር በርትተው እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል፡፡

ዶ/ር ፈለቀ ኮንፈረንሱን ሲያጠቃልሉ በመካከለኛና በረዥም ጊዜ ሊተገበሩ የታቀዱ እንዲሁም እስከአሁን መፍትሔ ያልተሰጣቸው የተወሰኑ የአጭር ጊዜ ተግባራት በቀጣይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራባቸው በመግለጽ የትምህርት ጥራቱን ለማስጠበቅ የትምህርት ልማት ሠራዊት ግንባታን ይበልጥ በማጠናከር የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ሁሉም ባለድርሻዎች በቅንጅት እንዲሠሩ አሳስበዋል፡፡

የግብርና ሣይንስ ኮሌጅ ዘርፈ ብዙ ምርምሮችን እያከናወነ መሆኑ ተገለፀ

Details
Thu, 23 July 2015 11:03 am

በዩኒቨርሲቲው የግብርና ሣይንስ ኮሌጅ በስሩ በተከፈቱ 7 የትምህርት መስኮች ዘርፈ ብዙ የምርምር ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህም ውስጥ በእንስሳት፣ በእፅዋት እና ደን ሳይንስ የትምህት ዘርፎች የሚካሄዱት ምርምሮች ለአብነት ተጠቃሽ ናቸው፡፡

የዕፅዋት ሣይንስ ትምህርት ክፍል ተጠሪ አቶ ኪያ አደሬ እንደገለጹት በትምህርት ክፍላቸው ጥራጥሬና ሰብሎችን አራርቆ መዝራት፣ ተፈጥሯዊና ዘመናዊ ማዳበሪያ አጠቃቀምን ጨምሮ የተለያየ እንክብካቤ በመስጠት የምርታማነት ዕድገትን ለመጨመር የሚያስችሉ ዘዴዎችን ለመለየት በትጋት እየተሰራ ነው፡፡

በዋናው ግቢ የእርሻ ምርምር ማሳያ ላይ እየተካሄደ ያለውን የሸንኮራ አገዳ ምርምር አስመልክተው ፕሮፌሰር አብዱል ቀይም ከሃን እንደተናገሩት ዩ ኤስ ኤን ጨምሮ ከተለያዩ 8 አገሮች የተሰባሰቡ 16 ዓይነት የሸንኮራ አገዳ ምርጥ ዝርያዎች እየተጠኑ ነው፡፡ ለወደፊትም ለኦሞ ኩራዝ፣ ለወንጂና ለመተሐራ ስኳር ፋብሪካዎች የተሻለ ግብዓት እንዲሆን ምርምሩን ስኬታማ ለማድረግ ከኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን ጋር በቅንጅት እየሠሩ መሆናቸውን ፕሮፌሰሩ ገልፀዋል፡፡

የደን ሣይንስ ትምህርት ክፍል ኃላፊ አቶ ዮናስ ኡጎ በበኩላቸው ትምህርት ክፍላቸው የአካባቢውን የደን ሀብት ለማሳደግ የሚያስችሉና ከአካባቢው የአየር ንብረት ጋር ተዛማጅ የሚሆኑ የዛፍ ዝርያዎችን በማጥናት ችግኝ አፍልቶ ለዩኒቨርሲቲው ካምፓሶችና ለአካባቢው ማኅበረሰብ የማድረስ ሥራ መጀመሩን ገልፀዋል፡፡ በዚህ ዓመት ከድሬዳዋ ተገዝቶ የመጣውን የእውነተኛ ኒም ዛፍ ችግኝ በማፍላት እስከ አሁን ከ14,000 በላይ ችግኞች የተሰራጩ ሲሆን በዘርፉ ቀጣይ ምርምሮችን በማካሄድ ከአንድ በላይ ጥቅም ሊሰጡ የሚችሉ ዛፎችን ለማስተዋወቅና ለማላመድ አቅደን እየሠራን ነው ብለዋል፡፡

የእንስሳት ሣይንስ ትምህርት ክፍል ኃላፊ አቶ ሠይፉ ብርሃኑ በትምህርት ክፍላቸው ምርጥ የወተት ላም ዝርያዎችን ከአካባቢው ዝርያዎች ጋር የማዳቀል ሥራ በቅርቡ የሚጀመር መሆኑን በመጥቀስ የእንስሳት መኖ ዕፅዋትን በማላመድ ለምርጥ የወተት ላሞችና ለዶሮ እርባታ ሥራዎች ግብዓት እንዲሆኑ ይደረጋል ብለዋል፡፡ የፕሮፌሰር ሰለሞን ‘chicken brooding box’ የተባለ ዘመናዊ የጫጩት ማሳደጊያ አጠቃቀም ጥናት እንደተጠናቀቀም ቴክኖሎጂው ለማኅበረሰቡ ተደራሽ ይሆናል፡፡

የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ነጂብ መሐመድ እንደተናገሩት ኮሌጁ ከተቋቋመ ገና ሁለት ዓመት ብቻ ቢሆነውም እየሠራቸው ያሉት ተግባራት ተስፋ ሰጪ ናቸው፡፡ ዲኑ በኮሌጁ ባሉት ሁሉም የትምህርት ክፍሎች በመምህራንና በተለይም በተመራቂ ተማሪዎች አበረታች ምርምሮች በመካሄድ ላይ መሆናቸውን ገልፀው የተጀመሩትና ሌሎችም አዳዲስ ምርምሮች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል፡፡

የተማሪዎች ኅብረት ለአረጋዊያንና ወላጅ አጥ ሕፃናት የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ የምሳ ግብዣ አደረገ፡፡

Details
Thu, 23 July 2015 11:02 am

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ኅብረት በአባያ ክ/ከተማ በኩልፎ ቀበሌ ለተገኙ በርካታ አረጋዊያንና ወላጅ አጥ ሕፃናት የ2007 ዓ.ም የፋሲካ በዓልን በማስመልከት የምሳ ግብዣ አድርጓል፡፡

“የሰጪ እጅ ሁሌም ከላይ ነው” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀውን የምሳ ግብዣ ያሰናዱት የተማሪዎች ኅብረት ፕሬዝደንት ተማሪ ጌትነት ዓለሙና የተማሪዎች ዲስፕሊን ተጠሪ ተማሪ ታመነ ዳኘው ናቸው፡፡ ተማሪ ጌትነት ባደረገው ንግግር የአ/ም/ዩን ተማሪዎች ወክሎ ከታዳሚዎቹ መሃል በመገኘት በዓሉን ማክበሩ እንዳስደሰተውና ለወደፊትም በተመሳሳይ መልክና የበለጠ አቅም በመፍጠር በዓላትን በጋራ ለማሳለፍ እንደሚሠሩ ተናግሯል፡፡

በአባያ ክ ከተማ የኩልፎ ቀበሌ ወጣቶችና ስፖርት ዘርፍ ኃላፊ ወጣት ተክሌ ብርሃነገነት እና የአርባ ምንጭ ከተማ ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ጽ ቤት ምኃላፊና የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ ወጣት በላይ ግዛቸው የአምዩ ተማሪዎች ኅብረት ያደረገውን ድጋፍ አመስግነው ለወደፊትም መሰል ትብብርና በጋራ የመሥራቱ ልምድ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡ በዝግጅቱ መጨረሻም የአ ም ዩ ተማሪዎች ኅብረት ለተሳታፊ ስፖንሰሮች የተሰጠውን የምሥክር ወረቀት ወስዷል፡፡

 

በተመሳሳይም የአ/ም/ዩ ከፍተኛ የአስተዳደር አካላት በ5ቱም ካምፓሶች ከተማሪዎች ጋር በመሆን የፋሲካን በዓል በድምቀት አክብረዋል፡፡ በዋናው ግቢ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ፈለቀ ወልደየስ ከሌሎች የአስተዳደር አካላት፣ የተማሪዎች ፕሬዝደንትና የተማሪዎች ተወካይ ኮሚቴዎች ጋር በመገኘት በዓሉ ደማቅ እንዲሆንና ተማሪዎች ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንዳሉ እንዲሰማቸው የሚያደርግ ድባብ ፈጥረዋል፡፡

በሌሎቹም ካምፓሶች የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ የኮሌጅ ዲኖችና የሥራ ክፍል ኃላፊዎች እንዲሁም የተማሪዎች ተወካዮች ከተማሪዎች ጋር በመሆን በዓሉ በልዩ ድምቀት እንዲከበር አድርገዋል፡፡

ሰላም ፎረም ለአባላትና ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ፡፡

Details
Thu, 23 July 2015 11:01 am

የዩኒቨርሲቲው ሰላም ፎረም ከግንቦት 22-23/2004 ዓ.ም በዋናው ግቢ በሰጠው ስልጠና በአምስቱም ግቢዎች የሚገኙ የተማሪዎች የሠላም ፎረም ፕሬዝደንቶችና አባል ተማሪዎች፣ አባል መምህራን፣ የካምፓስ አስተዳደሮች፣ የፀጥታና ደህንነት ሰራተኞች፣ዳይሬክተሮች፣ የጋሞ ጎፋ ዞን ፀጥታ አስተዳደር መምሪያ ተወካዮችና የሃይማኖት መሪዎች ተገኝተዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ፈለቀ ወልደየስ ስልጠናውን በንግግር ሲከፍቱ እንደገለጹት ከዚህ በፊት ከአገልግሎት አሰጣጥና ከሌሎች ጉዳዮች ጋር በተያያዘ አሳማኝ ባልሆኑ ምክንያቶች ግጭቶች ይነሱ እንደነበር በማስታወስ ይህ ፎረም ከተቋቋመ በኋላ ግን በርካታ ችግሮችን በመቅረፍ ለሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል፡፡

ከደቡብ ክልል ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ተወክለዉ የመጡት አሰልጣኝ አቶ ኃይሉ ማቲዮስ በበኩላቸው በክልላችን በሚገኙ ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ይህ መዋቅር አበረታች እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡አቶ ማቲዮስ አያይዘዉ አደረጃጀቱ ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ከመውረዱ በፊት ባለማወቅ ችግር ይፈጥሩ የነበሩ አንዳንድ ተማሪዎች ከጥፋታቸው ሙሉ በሙሉ በመዉጣት የሰላም አምባሳደር እስከ መሆን ደርሰዋል ብለዋል፡፡

የስልጠናዉ ትኩረት አቅጣጫ በዩኒቨርሲቲዉ ዉስጥ የሰላም ባህል እንዲጎለብት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ነዉ፡፡በወቅቱ ስለግጭት ምንነት፣መንስኤዎች፣አመላካች ሁኔታዎችና መፍትሄዎች ዙሪያ ሰፋ ያለ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ከተሳታፊዎች ለተነሱ በርካታ ጥያቄዎች አሰልጣኙ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

በስልጠናው ማጠናቀቂያ ወቅት ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት አሁን ላይ በዩኒቨርሲቲው እየተካሄደ ያለዉ የመማር ማስተማር ሥራ አስደሳች መሆኑን በመጥቀስ ለወደፊቱም ሁሉም ተማሪ ለዩኒቨርሲቲዉ ሰላም በጋራ ኃላፊነት ሊወስድ ይገባል ብለዋል፡፡

  1. የኮምፒዉተር ሳይንስ ትምህርት ክፍል ተማሪዎች የአይ ሲ ቲ አዉደ-ርዕይ አቀረቡ፡፡
  2. 24ኛው የግንቦት 20 የድል በዓል በዋናው ግቢ በድምቀት ተከበረ
  3. Guidance, hard works and determination is the key: AMU topper
  4. INSTITUTE AND COLLEGE-WISE LIST OF TOP-SCORING STUDENTS

Page 461 of 523

  • 456
  • 457
  • 458
  • 459
  • 460
  • 461
  • 462
  • 463
  • 464
  • 465

Downloads

  • Newsletter
  • Registrar
  • Academic Calendar
  • Finance & Budget Transparency

Quick Links

  • News
  • Vacancies
  • AMU Intranet
  • ICT Center

Systems

  • SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning
  • Facebook
  • X
  • Telegram
  • Youtube
  • Email

Contact us

Corporate Communication
P.O. Box 21
Arba Minch University

Tel: +251-46881-4986
Fax: +251-46881-0820/0279
E-mail: corcom@amu.edu.et , ictc@amu.edu.et

Registrar

  • About Us
  • Alumni
  • Alumni Registration
  • Contact us

Colleges

  • Agriculture
  • Business & Economics
  • Medicine and Health Sciences
  • Natural Sciences
  • Social Sciences & Humanities

Systems

  • SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning

Copyright © 2025 Arba Minch University. 

  • Campus Guide
  • Contact Us
  • Sitemap