- Details
አርባ ምንጭ የዩኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት ከተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብት ከፍተኛ ኮምሽን ጋር በመተባበር በሽግግር ፍትሕ ሂደት ዙሪያ ወጣቶች፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች መምህራን እንዲሁም ተማሪዎች ያላቸውን ሚና አስመልክቶ ሚያዝያ 15/2016 ዓ/ም ገለጻ አካሂዷል፡፡
Read more: የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት በሽግግር ፍትሕ ሂደት ዙሪያ ገለጻ አደረገ
- Details
በ17/08/2016 ከ8:00 ጀምሮ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ ለዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች በኢንተርፕርነርሽፕ ዙሪያ ያተኮረ ልዩ መርሃ ግብር ተዘጋጅቷል። በዝግጅቱ ላይ ታዋቂው የቢዝነስ አማካሪ እና ደራሲ ዶ/ር ወሮታው በዛብህ ተገኝተው የኢንተርፕርነርሽፕ የተግባር ተሞክሯቸውን ያካፍላሉ። በተጨማሪ በዕለቱ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መካከል የቢዝነስ ሃሳብ ውድድር ይካሄዳል። የተሻለ ሃሳብ ያቀረቡ ተማሪዎችም ይሸለማሉ:: ስለሆነም ሁሉም የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በዚህ ሁነት ላይ እንድትገኙ የተጋበዛችሁ መሆኑን እናሳውቃለን።
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኅበራዊ ሳይንስና ሥነ ሰብ ኮሌጅ በደቡብ ኦሞ ዞን ያንጋቶም ወረዳ በሚነገረው የኩዌጉ ቋንቋና ባህል ስነዳ እና ትንተና ላይ ጥናት ለማካሄድ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ሚያዝያ 12/2016 ዓ/ም የፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር አካሂዷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: የኩዌጉ ቋንቋና ባህል ስነዳ እና ትንተና ላይ ጥናት ለማካሄድ የመክፈቻ መርሃ ግብር ተካሄደ
- Details
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ማስ/ጽ/ቤት ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት እና ከጋሞ ዞን ጋር በመተባበር የግድቡ ግንባታ የተጀመረበት 13ኛ ዓመት በዓል ምክንያት በማድረግ «የአባይ ዘመን ትውልድ ታላቅ የሥነ ጽሑፍ ምሽት» “በኅብረት ችለናል!” በሚል መሪ ቃል ግንቦት 09/2016 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው ያካሂዳል፡፡ በዕለቱ መርሃ ግብር ላይ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ ግጥሞችንና አጭር ትውን ተውኔቶችን ማቅረብ የምትችሉ ተማሪዎች የሥነ ጽሑፍ ሥራዎቻችሁን ዩኒቨርሲቲው አወዳድሮ ከ1ኛ - 3ኛ የወጡ የተማሪዎች የሥነ ጽሑፍ ሥራዎች በመድረኩ እንዲቀርቡ ዕድል ለመስጠት ስለተፈለገ ከሚያዝያ 15-30/2016 ዓ/ም ድረስ ሥራዎቻችሁን በዩኒቨርሲቲው ኢ-ሜይል አድራሻ፡- This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. ወይም This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. በመላክ ወይም የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጽ/ቤት የመወዳደሪያ ጽሑፋችሁን በሶፍት ኮፒ በመያዝ በአካል በማቅረብ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እየገለጸ ተማሪዎቻችን ዕድሉን በማግኘትና በዚህ ሀገራዊ መድረክ ላይ በመገኘት በሥነ ጽሑፍ ጥበብ የበኩላችሁን መልዕክት እንዲታስተላልፉ ከወዲሁ ያሳውቃል፡፡