በውኃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የማኅበረሰብ ጉድኝት ዘርፍ እየተከናወኑ ያሉ ሦስት ፕሮጀክቶች የደረሱበት ደረጃ የመጀመሪያ ዙር ግምገማ የካቲት 08/2016 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የጋሞ ዞን ኢንቨስትመንትና ኢንደስትሪ መምሪያ የጫሞ ሐይቅ ረግረጋማ ስፍራን/Buffer Zone/ መልሶ ለማልማትና ለመጠበቅ የሚያስችል 1.65 ሄክታር ተጨማሪ መሬት ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ /AMU-IUC/፣ ጋንታ አባ እና ባይራ ለተሰኙ ማኅበራት የካቲት 08/2016 ዓ/ም አስረክቧል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ያሠለጠናቸውን የሕክምና ዶክተሮች ለ9 ጊዜ የካቲት 16/2016 ዓ.ም ያስመርቃል፡፡ የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ በዋናው ግቢ መግቢያ በር አካባቢ በሚገኘው አዳራሽ ከጧቱ 2፡00 ጀምሮ የሚካሄድ ይሆናል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከኮንሶ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ጋር በመተባበር በሰብአዊ መብት አያያዝና አጠባበቅ እንዲሁም በሰላም እሴት ግንባታ ዙሪያ በኮንሶ ዞን ለሚገኙ 250 የፖሊስ አባላት ከየካቲት 6-9/2016 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ክርስቲያን ኤይድ/Christian Aid/ እና ሶስ ሳህል /SOS Sahel Ethiopia/ ከተሰኙ ግብር ሰናይ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ከተለያዩ ዞኖች ለተወጣጡ ማኅበራት ተወካዮችና ሥራ አጥ ወጣቶች ለ10 ቀናት የሚቆይ  የአሠልጣኞች ሥልጠና ከጥር 29/2016 ዓ/ም ጀምሮ እየሰጠ ይገኛል፡፡ ሥልጠናው የእንሰት ተረፈ ምርት ከሆነው ቃጫ ዕሴት የተጨመረባቸውና የተሻለ ዋጋ የሚያወጡ ጌጣጌጦችንና ሌሎች ቁሳቁሶችን ማምረት የሚያስችል ነው፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡