አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከ “SNV-Rayee” ማስተርካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር በአርባ ምንጭ ከተማ ለሚገኙ ወጣት ሥራ ፈጣሪዎች የቢዝነስ ሃሳብ ውድድር ያዘጋጀ በመሆኑ መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች በውድድሩ ተሳታፊ እንድትሆኑ ተጋብዛችኋል፡፡

Arba Minch University is interested to recruit academic staffs for Sawla Campus in the following position and fields.

Position: - Assistant Lecturer (BA), Lecturer & Above

Qualification: - M.Sc./MA/MD/LLM/Ass. Prof., PhD & Above

Requirement: - CGPA≥3.50 for Postgraduate studies, Research Result: Very Good and above. Click here to see more Photos. 

ዕጩ ዶ/ር ማቲዎስ አግዜ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በባዮሎጂ ት/ክፍል በ ̋Biodiversity Conservation and Management” ትምህርት ፕሮግራም የ3ኛ ዲግሪ ትምህርቱን ሲከታተል ቆይቷል፡፡ ዕጩ ዶ/ር ማቲዎስ የ3ኛ ዲግሪ መመረቂያ ጽሑፉን የውስጥና የውጪ ገምጋሚዎች እንዲሁም አማካሪዎች በተገኙበት በዓባያ ካምፓስ አዲሱ የአስተዳደር ሕንጻ አዳራሽ ነሐሴ 29/2015 ዓ/ም ከጧቱ 2፡30 ጀምሮ የሚያቀርብ ይሆናል፡፡

በአዲሱ የፌዴራል መንግሥት መዋቅራዊ አደረጃጀት ለውጥ መሠረት በሠራተኞች የድልድል አፈጻጸም መመሪያ ዙሪያ በሁሉም ካምፓስ ለሚገኙ የአስተዳደር ሠራተኞች ከነሐሴ 16-19/2015 ዓ/ም ድረስ ገለጻ ተደርጓል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጀርመን ሀገር ከሚገኘው ዓለም አቀፍ ሮትራክት ድርጅት/Rotary Club Bonn International/ እና ሮተሪ ኢትዮጵያ/Rotary Ethiopia/ ጋር በመተባበር ‹‹Environmental Sustainability, Water and Agroforestry with Permaculture for Gircha in Ethiopia›› የተሰኘና ለሦስት ዓመታት የሚቆይ አዲስ የትብብር ፕሮጀክት በቆጎታ ወረዳ ነሐሴ 20/2015 ዓ/ም ይፋ አድርጓል፡፡ በግብርናና ደን፣ አፈርና ውሃ ጥበቃ፣ ንጽሕናው የተጠበቀ የቤት አሠራርና አያያዝ እና የሶላር ፕላንቶች ጥገና ላይ ሥልጠናዎችን መስጠት፣ በማኅበረሰቡ ቤቶች አስተማሪ ፖስተሮችን ማቅረብ እንዲሁም ለፕሮጀክቱ ውጤቶች ዘላቂነት ትብብሮችን መመሥረት በፕሮጀክቱ ከሚተገበሩ ሥራዎች መካከል ይጠቀሳሉ፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ