አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ10 ደቂቃ አንድ ኩንታል በቆሎ መፈልፈል የሚችል ማሽን ሠርቶ የካቲት 02/2016 ዓ/ም በጋሞ ዞን ካምባ ዙሪያ ወረዳ ጋርሳ ሀኒቃ ቀበሌ ሶቦ መንደር ለሚገኙ አርሶ አደሮች ለሙከራ አቅርቧል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባባር ‹‹Building Information Management/BIM›› በሚል ርእስ ለአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ እና ውኃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች መምህራን፣ ለዩኒቨርሲቲው ፋሲሊቲ አስተዳደርና የግንባታ ጽ/ቤት ባለሙያዎች ከጥር 13 - 30/2016 ዓ/ም የግንባታ ሞዴሊንግ ቴክኖሎጂን አስመልክቶ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ የኒቨርሲቲ የፀረ ሙስናና ሥነ ምግባር መከታተያ ዳይሬክቶሬት ለጫሞ፣ ዓባያና ሳውላ ካምፓሶች አዲስ ገቢ ተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ዲስፕሊን መመሪያ ላይ ከጥር 25 - የካቲት 02/2016 ዓ/ም የሚቆይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

ዩኒቨርሲቲው ከአርባ ምንጭ ፖሊ ቴክኒክና ሳታላይት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን የማንጎ ማውረጃ ቴክኖሎጂ ጥር 28/2016 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ኦቾሎ ላንቴ ቀበሌ ለሚገኙ አርሶ አደሮች ለሙከራ አቅርቧል፡፡ የቴክኖሎጂዎቹን አጠቃቀም አስመልክቶ በባለሙያዎች ገለጻ በማድረግ ሁለት የማውረጃ መሣሪያዎችን በቡድን የተከፈሉ አርሶ አደሮች የተረከቡ ሲሆን ከአርሶ አደሩ የሚመጣውን ግብረ መልስ ተከትሎ ማሻሻያ ታክሎ በስፋት ለማዳረስ እንደሚሠራ ተገልጿል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በምርምር ማስተባበሪያ ጽ/ቤት አዘጋጅነት ከተለያዩ የትምህርት ክፍሎች ለተወጣጡ የኮሌጁ መምህራንና ተመራማሪዎች ከጥር 23 - 26 ለአራት ተከታታይ ቀናት የጂአይኤስ አጠቃቀም ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡